በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ፍራፍሬ አምራች የደቡብ አፍሪካ ገበሬዎች ተጎድተዋል

Your browser doesn’t support HTML5

ሩሲያ በዩክሬን ላይያደረሰችው ወረራ ደቡብ አፍሪካውያን የፍራፍሬ አምራች ገበሬዎችን እያስከፋ ነው። በወረራው ምክንያት ሩሲያ ላይ በተጣሉባት ማእቀቦች ሳቢያ ገበያዎቹዋ በመዘጋታቸው በደቡብ አፍሪካ አምራቾች ላይ የብዙ ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ ደቅኖባቸዋል። ደቡብ አፍሪካ እንደብርቱካን እና ሎሚ የመሳሰሉ ፍራፍሬዎችን ለዓለም ገባያ በብዛት በማቅረብ ሁለተኛ ሀገር ስትሆን ገበሪዎቹ ሌላአማራጭ ገበያ እንዲፈልጉ ተገድደዋል።