የኦሮምያ መደበኛ ያልሆኑ ችሎቶች

Your browser doesn’t support HTML5

ኦሮምያ ክልል ውስጥ ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ከሁለት መቶ በላይ ወረዳዎች ውስጥ ሥራ መጀመራቸው ተገልጿል።

የፍርድ ቤቶቹ በቀበሌና በወረዳዎች ደረጃ ሥራ መጀመር “የኅብረተሰቡን እንግልት አስቀርቷል፣ የፍርድ ቤቶችን ጫና ቀንሷል” ሲል የኦሮምያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታውቋል። መደበኛ ያልሆኑት ባህላዊ ችሎቶች አጋዥ የፍትህ አገልግሎት እንዲሰጡ የክልሉ ምክር ቤት ባለፈው ዓመት ባወጣው አዋጅ ነበር።

ፍርድ ቤቶቹ ሥራ ከጀመሩባቸውና አገልግሎት እየሰጡ ካሉባቸው አካባቢዎች በኦሮምያ ልዩ ዞን ዱከም ከተማና አቃቂ ወረዳ የሚገኙ ሲሆን “ፍርድ ቤቱ የተደበቀ እና ምስክር በሌለበት ለተፈፀመ ወንጀል ሁሉ ፍትኅ የሚገኝበት ሆነው እንዳገኙት ነዋሪዎች ተናግረዋል።