ኦፌኮ የኦነግን ባንዲራ እንዳይጠቀም ኦነግ ጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ የኦነግን ሰንደቅ ዓላማ እንዳይጠቀም ኦነግ የጠየቀው በአባላቱ ጥያቄ መሠረት መሆኑን ገልጿል።
ደብዳቤው በሁለቱ ፓርቲዎች ግንኙነት ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ ይኖራል ብለው እንደማያምኑ የኦነግ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ ተናግረው የተፃፈው ለግልፅነት ሲባል ነው ብለዋል።
ኦፌኮ በጉዳዩ ላይ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።