አቶ በቀለ ገርባ በትናንትናው ዕለት ከእሥር ሲፈቱ የተደረገላቸው አቀባበል

Your browser doesn’t support HTML5

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ በትናንትናው ዕለት ከእሥር ሲፈቱ በሀገሪቱ የተለያዩ ስፍራዎች የደስታ መግለጫ ሰልፎች እንደነበረ ሲገለፅ አብዛኞቹ በኦሮምያ ክልል ናቸው፡፡ የኦሮሞ ፌድራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ ከእስር ከወጡ በኋላ ወደ አዳማ መኖሪያ ቤታቸው ሲያመሩ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ በየጎዳናው በመውጣት፣ በተሽከርካሪዎች በማጀብ አቀባበል አድርጎላቸዋል፡፡