መንግሥት ለሳውዲ እስረኞች ትኩረት እንዲሰጥ ኦፌኮ ጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

በሳውዲ አረብያ እስር ቤት ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን መንግሥት አስቸኳይ እርዳታ እንዲያደርግላቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ ጠየቀ። የፓርቲው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጥሩነህ ገምታ ፓርቲያቸው መንግሥት የሚያስቀምጠውን አቅጣጫ ተከትሎ ለእነዚህ ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል ። የኢትዮጵያ መንግሥት በሳውዲ በእስር ቤትና ከእስር ቤት ውጭ በሚገኙ የኢትዮጵያ ዜጎች ላይ ሲነጋገር መቆየቱን በቅርቡ አስታውቋል።