የሴቶች የወር አበባ ዑደት ማቆም የሚያስከትለው አካላዊና ስነልቦናዊ ለውጥ

Your browser doesn’t support HTML5

የሴቶች ወርሃዊ የተፈጥሮ ዑደት ማቆም በአብዛኛው ከ 40 ዓመት በኋላ የሚጀምር ሲሆን፤ የሴቷ የእርግዝና እና የመውለጃ ወቅት ማብቃቱ የሚታወቅበት ሂደት ነው፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ውስጥም ሴቷ በብዙ አካላዊና ስሜታዊ ለውጦች ውስጥ የምታልፍ ሲሆን፤ የሰውነት በድንገተኛ እና ከፍተኛ ሙቀት ውስጥ ማለፍ፣ የስሜት መለዋወጥ፣ እንቅልፍ ማጣት እና ቁጡነት ዋነኞቹ ናቸው፡፡