የናይል ተፋሰስ ሚኒስትሮች ተሰበሰቡ

  • ቪኦኤ ዜና

ጁባ - ደቡብ ሱዳን

ደቡብ ሱዳን በናይል ወንዝ ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ለመገንባት 16 ቦታዎችን መምረጧል አስታወቀች፡፡



የናይል ተፋሰስ ሃገሮች


Your browser doesn’t support HTML5

የናይል ተፋሰስ ሚኒስትሮች ተሰበሰቡ


ደቡብ ሱዳን በናይል ወንዝ ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ለመገንባት 16 ቦታዎችን መምረጧል አስታወቀች፡፡

ባለ አምስት ቢሊየን ዶላር መዋዕለ-ነዋዩ ኅዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ጎረቤቶች ቀልብ አነቃቅቶና ውዝግቦችም እየተሰሙ ባሉበት ሁኔታ ውስጥ በአባይ ውኃ አጠቃቀም ላይ ለመምከር የአባይ ተፋሰስ ሃገሮች ድርጅት ስብሰባ ደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ላይ ዛሬ ተሰብስበዋል፡፡

የኅዳሴ ግድብ ወደ ግብፅ የሚወርደውን ውኃ መጠን ይቀንስብናል ሲሉ ግብፃዊኑ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ሥጋታቸውን በየጊዜው እየገለፁ ነው፡፡

ከናይል ተፋሰስ ሃገሮች የምክክር ስብሰባዎች አንዱ

በዚህ ወር መጀመሪያ ደግሞ የግብፅ ፕሬዚዳንት ሞሐመድ ሞርሲ በውኃ ደኅንነታቸው ላይ የሚፈጠርን “ማንኛውንም ሥጋት ለመያዝ ‘ሁሉም አማራጮች ክፍት’ ናቸው” ባሉ ጊዜ በውኃው አቅርቦት ላይ ያላቸውን ፍርሃት ጠቁመው እንደነበርና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ በሰጡት ምላሽ የግብፅ መሪዎች “… ካላበዱ በቀር የጦርነትን አማራጭ ይወስዳሉ ብለን አናምንም …” ብለው ነበር፡፡

የናይል ተፋሰስ ሃገሮች

በናይል ሃገሮች መካከል የሰፋ ትብብር እንዲፈጠር የአሥር የተፋሰሱ ሃገሮች ሚኒስትሪዎችን መሪዎች የጁባ ስብሰባ በከፈቱ ጊዜ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ተጠሪው ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን ጥሪ አሰምተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር አቶ አለማየሁ ተገኑም ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ የጀመረችውን ግድብ ግንባታ ሥራ እንደማታቆም አስታውቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የማንንም ሃገር የመሻሻል ዕድል እንደማትቃወም የተናገሩት የግብፅ የውኃ ኃብቶች ምክትል ሚኒስትር አሕመድ ባህ ኤልዴይን ይሁን እንጂ ናይል ወንዝን በተመለከተ ማንኛቸውም ዕቅዶች ከመነደፋቸው በፊት መዘዞች ሁሉ ግምት ውስጥ ሊገቡ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡

ለዝርዝሩ ዘገባውን ያዳምጡ፡፡