የዓመት በዓል ገበያ - በአምቦ

Your browser doesn’t support HTML5

የአዲሱ 2013 ዓ.ም. የዋዜማ ገበያ ደማቅ መሆኑን አንዳንድ የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። የቪኦኤ ዘጋቢ በዶሮ፣ በግ እንዲሁም ሽንኩርት ተራ ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ሸማቾችና ሻጮች ግብይቱ በጥሩ ሁኔታ ቢከናወንም ሰዎች ራሳቸውን ከኮሮናቫይረስ እየተከላከሉ አይደለም ሲሉ ትዝብታቸውን ገልፀዋል።