ነቀምቴ ላይ አራት ከፍተኛ ሐኪሞች ታሥረዋል፤ አንድ ኮሪያዊ ተሰናብተዋል

ነቀምቴ

ከነቀምቴ ሆስፒታል አራት ሃኪሞች ታስረው በነቀምቴው የምሥራቅ ወለጋ ማረሚያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡



Your browser doesn’t support HTML5

ነቀምቴ ላይ አራት ከፍተኛ ሐኪሞች ታሥረዋል



ዶ/ር አዳም ለማ፤ የቀዶ ሕክምና ሐኪም፣ ዶ/ር ኢሣያስ ብርሃኑና ዶ/ር በላይ ቤተማርያም የማኅፀንና የፅንስ ስፔሻሊስቶች፣ ዶ/ር ታመነ አበራ፤ ቀድሞ የሆስፒታሉ የሕክምና ዳይሬክተርና አሁን ለስፔሻላይዜሽን የጥቁር አንበሣ ሬዚደንት ሐኪም፣ እንዲሁም ዶ/ር ሪም ጆንግ ሆ፤ ኮርያዊ የአጥንት ሐኪም፡፡
ሁሉም በነቀምቴ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ አገልግለዋል፡፡

ዛሬ ኮርያዊው ሐኪም ከሥራ ሲሠናበቱ አራቱ ኢትዮጵያዊያን ግን በቁጥጥር ሥር ውለው ነቀምቴ በሚገኘው ማረሚያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡

ፈታሾች በዶ/ር አዳም ለማ ወላጆች ቤት - አዲስ አበባ


የእነዚህ ለረዥም ዓመታት አገልግሎት ሰጥተዋል የሚባሉ ሐኪሞች ከሥራቸውና ከደመወዛቸው መታገድ፣ አልፎም መታሠር መነጋገሪያ እየሆነ ነው፡፡

“ጥፋታቸው” የተባለው ምን ይሆን? በአካባቢያቸው ያሉ ሰዎችስ “ጥፋተኛ ናቸው” ብለው ያምናሉ?

የተያያዘው ዘገባ የፖሊስን፣ የሆስፒታሉን አስተዳደር፣ የእሥረኞቹን ሐኪሞች ቤተሰቦችና ጠበቃ የሚሉትን ይዞ ዝርዝር መረጃ ይሰጥዎታል፡፡
ያዳምጡት፡፡