ኔቶ

Your browser doesn’t support HTML5

የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ሀገሮች ድርጅት/ኔቶ/ሰባኛ ዓመት ለማክበር ለንደን በተደረገው የመሪዎች ጉባዔ ጥሩ ውጤት እንደታየበት የድርጅቱ አባል ሀገሮች ባለሥልጣኖች ገልፀዋል፡፡ መሪዎቹ ማንኛውንም ዓይነት ከሩስያ የሚቃጣባቸውን ወረራ በኅብረት ለመከላከል ያላቸውን ቁርጠኛነት በአዲስ መልክ አረጋግጠዋል፡፡ ይሁንና ጉባዔው በመሪዎች መካከል በተንፀባረቀው መቃቃርና የካናዳ ጠ/ሚኒስትር ያልተሰሙ መስሏቸው በተናገሩት ነገርም ሊታወስ እንደሚችል ተዘግቧል፡፡