የሃገር ሽማግሌዎች ሊካሄድ ስለታቀደው ብሔራዊ መግባባት ምን ይላሉ?

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ለማካሄድ ላቀደችው አገራዊ ምክክር ኮሚሽን አቋቁማ የኮሚሽኑን መሪዎች መርጣለች። ዛሬ በአስቸኳይ የተሰበሰበው የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ እና አካታች ምክክር እንዲያካሄድ በአዋጅ ለተቋቋመው ኮሚሽን በኮሚሽነርነት የሚያገለግሉ 11 ግለሰቦችን ሹመት አጽድቋል። ይህ ሃገራዊ ምክክር የታሰበውን ሰላም ያመጣል ወይ? መፍትሔስ ይሰጣል ወይ? ስንል የሃገር ሸማግሌዎች እና የተወሰኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ጠይቀናል።