የድሬዳዋ ከተማ ተወላጆችን ያሰባሰበው “ናፍቆት ድሬ”

Your browser doesn’t support HTML5

“ናፍቆት ድሬ” በሚል ሐሳብ ከመላው ዓለም የተሰባሰቡ የድሬዳዋ ተወላጆች ከተማዋ ላይ ተሰባስበው ነበር። በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከተማዋን ለቀው የወጡ የቀድሞ ነዋሪዎቿ ከተለያዩ ቦታዎች ተሰባስበው ዳግም የተገናኙበት ዝግጅት ነበር። በዚህ ዝግጅት ላይ የተሳተፉት የቀድሞ የከተማዋ ነዋሪዎች ቀድሞ የሚያውቁትን የከተማዋን ገፅታ ከአሁኑ ጋራ እያነፃፀሩ እንዲነግሩን ጠይቀናቸዋል።