ሚቱ ከአንድሩው ኮሞ በኋላ

Your browser doesn’t support HTML5

ከአስር ዓመታት በላይ በኒው ዮርክ ሃገረ ገዥነት የቆዩት አንድሩው ኮሞ በቀረቡባቸው የወሲባዊ ትንኮሳ ውንጀላዎች የተነሳ ሥራቸውን ለቅቀዋል።
ይህ የሆነው የወሲባዊ ጥቃት እና ወሲባዊ ትንኮሳን ለመታገል ሚቱ በመባል የሚታወቀው ንቅናቄ በተመሰረተ በአራት ዓመቱ መሆኑ ነው።
የወሲባዊ ወከባ አድራጎቶች ለማስወገድ ያለመው የሚቱ ዘመቻ እስካሁን ምን አከናወነ፣ ወደፊትስ ምን ማከናወን ይኖርበታል፤ የሚሉትን ጥያቄዎች የአሜሪካ ድምጿ ካሮላይን ፕረሱቲ ባጠናቀረችው ዘገባ ተመልክታዋለች።