በመቐለ ሁለተኛው ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ሥነ ሥርዐት ተከናወነ

Your browser doesn’t support HTML5

ትላንት ሰኞ፣ ሚያዝያ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በመቐለ ከተማ የሰማዕታት ጎዳና፣ በሺሕዎች የሚቆጠሩ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች የተሳተፉበት ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ሥነ ሥርዐት ተከናውኗል፡፡

የኢፍጣር መርሐ ግብሩ ተሳታፊ የነበሩ አማኞች፣ መርሐ ግብሩን ማካሔድ የቻልነው፣ “ሰላም በመስፈኑ ነው፤” ብለዋል፡፡ ይህም ሰላም፣ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተሳታፊዎቹ አሳስበዋል፡፡