ከመቐለ ወደ አዲስ ኣበባ በሚደረግ በረራ የተጣለ ገደብ እንደሌለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመቐለ ወደ አዲስ ኣበባ በሚደረግ በረራ "ከዕድሜ ጋር ተያይዞ ተጓዦች ላይ የጣለኩት ምንም ዓይነት የበረራ ገደብ የለም" ሲል አስታወቀ።

የአሜሪካ ድምፅ በመቐለ አየር ማረፊያ አግኝቶ ያነጋገራቸው ወጣቶች በበኩላቸው "በዕድሜያችን ምክንያት እንዳንጓዝ እንቅፋት እየገጠመን ነው" ብለዋል።

በሌላ በኩል የትግራይ ክልል የመንገድ፣ ትራንስፖርትና ኮንስትራክሽን ቢሮ 'ቅድሚያ አገልግሎት ማግኘት ለሚገባቸው ነው አገልግሎት እየተሰጠ ያለው' ብሏል።