40 የሚሆኑ ሜዲቴራኒያን ባሕርን ሊያቋርጡ ሲሞክሩ ሰመጡ

Your browser doesn’t support HTML5

ሜዲቴራኒያን ባሕርን ሊያቋርጡ የነበሩ አርባ የሚሆኑ ሰዎች ትናንት /ማክሰኞ/ መስጠማቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር አስታወቀ። ሰዎቹ የተነሱት ከሊብያ ዋና ከተማ ትሪፖሊ በስተምሥራቅ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኝ አል-ኾምስ ከተማ ነበር።