በትሪፖሊ ውጊያ ብዙ ህይወት ጠፋ

Your browser doesn’t support HTML5

የሁለቱ የሊቢያ ተቀናቃኝ መንግሥቶች ታማኝ ሚሊሽያዎች ዋና ከተማይቱ ትሪፖሊ መሀል ላይ ባካሄዱት ውጊያ ብዙ ሰው መገደሉን የሃገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።

ምሥራቃዊውን የአገሪቱን ክፍል የያዙት የጠቅላይ ሚኒስትር ፋቲ ባሻጋ ደጋፊዎች የዋና ከተማይቱን አንዳንድ ክፍሎች ሲቆጣጠሩ ከተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ ድቢባህ ወገን የሆኑ ኃይሎች በበኩላቸው አሁንም ስፋት ያለውን አካባቢ እንደያዙ መሆናቸው ተገልጿል።