የሊቢያ የባሕር ዳርቻ ጠባቂዎች መቶ አፍሪካዊያን ፍልሰተኞችን ከሞት ታደጉ

Your browser doesn’t support HTML5

መቶ አፍሪካውያን ፍልሰተኞች በጀልባ ተጭነው አውሮፓ ሲጓዙ ከመስጠም መትረፋቸው ተገለፀ፡፡ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከሊቢያ ተነስተው ወደ አውሮፓ ጉዞ የጀመሩት ፍልሰተኞች ከባህር ከመስጠም ያዳኗቸው የሊቢያ ባሕር ጠባቂዎች ሲሆኑ፣ አብዛኞቹ ሴቶችና ሕፃናት ናቸው፡፡ ከኤርትራና ከሶማልያ የተነሱት ፍልሰተኞች ከምሥራቅ ሊቢያ ኪምሶ ከተማ ተነስተው ወደ አውሮፓ ጉዞ እያደረጉ ነበር፣ በባሕር ላይ እያሉ የጀልባው ሞተር የጠፋው፡፡