ኢሰማኮ በትግራይ ክልል የነበሩ በሺሆች የተቀጠሩ አባሎቹ የት እንዳሉ እንደማያውቅ ገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፈደሬሽ (ኢሰማኮ) በትግራይ ክልል ነበሩኝ ያላቸው 70 ሺህ የሚሆኑ አባሎቹ የት እንዳሉ እንደማያውቅ አስታወቀ፡፡ የኮንፈደሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት አስተያየት በጦርነቱ ምክንያት ከትግራይ ክልል ኢንዱስትሪዎች የተበታተኑት አባላቱ የት እንደሚገኙና በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ ለማወቅ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት እንደሚደርግ ገልፀዋል፡፡ የኮንፈደሬሽኑ አባላት በትግራይ ክልል ጉብኝት ማድረጋቸውን የገለፁት አቶ ካሳሁን፣ በአካል የተመለከቱዋቸው ፋብሪካዎች ሙሉ በሙሉ የወደሙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።