ከተራ አዲስ አበባ ውስጥ በድምቀት እየተከበረ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ምዕመናን ከአዲስ አበባ አድባራት ለበዓለ ጥምቀቱ የወጣውን ታቦት አጅበው ጃን ሜዳ ጥምቀተ-ባህር አሳርፈዋል።
ታቦታቱ በካህናት፣ በዲያቆናት፣ በመዘምራንና በምዕመናን ታጅበው ጥምቀተ-ባህሩ ማደሪያቸው ከደረሱ በኋላ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ኃላፊ ሊቀ ኃይላት ቀሲስ በላይ መኮንን መልዕክት አሰምተዋል።

የዘንድሮው የከተራ በዓል ኢትዮጵያ ከብዙ ችግሮች እየወጣች ባለበት ጊዜ እየተከበረ መሆኑን ሊቀ ኃይላት ቀሲስ በላይ አስታውሰው ፈታኝ ከሆነው የኮሮናቫይረስ ምዕመናን እንዲጠበቁ አሳስበዋል።

የጥምቀቱን ታሪክም አስተምረዋል።
ጥር 10/2014 ዓ.ም