ራዕይ ፓርቲ ዘጠኝ ፓርቲዎች አባል ከሆኑበት አገረአቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክርቤት ራሱን ማግለሉ ኣስታወቀ

  • ሰሎሞን ክፍሌ

የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከአቶ ተሻለ ሠብሮ

ራዕይ ፓርቲ ኢሕአዴግን ጨምሮ ዘጠኝ ፓርቲዎች አባል ከሆኑበት አገርአቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት ራሱን ማግለሉን አስታውቋል። ለምን?

“ምክር ቤቱ እየሠራ ያለው፥ በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጁና በአገርአቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መተዳደሪያ ደንብ መሠረት አይደለም” በሚል ፓርቲው ራሱን ማግለሉ ይገልጻል።

ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ባለው የተቃውሞ እንቅስቃሴና በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ጉዳይ ላይ ለመነጋገር አቅርቤ ነበር የሚለው ጥያቄም ተቀባይነት እንዳላገኘ ፓርቲው በማሳያነት ጠቅሷል።

ከኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ /ኢራፓ/ ሊቀ መንበር ከአቶ ተሻለ ሠብሮ ጋር የተካሄደው ቃለ-ምምልስ ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ራዕይ ፓርቲ ዘጠኝ ፓርቲዎች አባል ከሆኑበት አገረአቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክርቤት ራሱን ማግለሉ ኣስታወቀ