ዩናይትድ ስቴትስ ከኢንዶኔዥያ ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ለማሳደግ ያላትን ዕቅድ አስታወቀች
Your browser doesn’t support HTML5
የዩናይትድ ስቴትሱ የመከላከያ ሚንስትር ጂም ማቲስ ሀገራቸው ከኢንዶኔዥያ ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ለማሳደግ ያላቸውን ዕቅድ አስታወቁ። ምን ዓይነት የትብብር ሥራዎችን መሥራት እንደሚችሉ የተሻለ ሃሳብ ያላቸው መሆኑን ተናገሩ።
በሌላ በኩል የኢንዶኔዥያ ልዩ ኃይል፤ በአሁኑ ወቅት ለሥራ ጉብኝት ከዚያ ለሚገኙት የዩናይትድ ስቴትሱ የመከላከያ ሚንስትር ጂም ማቲስ የተቀነባበረ የፀረ ሽብር መልሶ ማጥቃት ትርዒት አሳይቷል።