ወደ አዲስ አበባ ይጓጓዙ የነበሩ ፈንጂዎች ተያዙ

Your browser doesn’t support HTML5

በተለምዶ "ቆራሊዮ" እየተባለ የሚጠራውን የወዳደቁ ብረቶች አስመስሎ ከሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ወደ መሃል ሃገር ሊገቡ የነበሩ 23 ሳጥን ፈንጅዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ ግዙፍ ህንጻዎችንና ድልድዮችን ማፍረስ እንደሚችሉ የሚነገርላቸው ፈንጅዎች በሰሜን ወሎ ጉባ ላፍቶ ወረዳ ከትናንት በስቲያ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡