ኢትዮጵያ በሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር በየዓመቱ 3.3 ቢሊዮን ዶላር ታጣለች

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ፣ በሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር ምክንያት፣ በየዓመቱ 3ነጥብ3 ቢሊዮን ዶላር እንደምታጣ አንድ ጥናት አመለከተ፡፡ በሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር ላይ የተደረገው ይኸው ጥናት፣ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት ከሚላከው ገንዘብ 78 በመቶ የሚኾነው፣ ከባንክ ውጭ ባሉ ሕገ ወጥ መንገዶች በኩል እንደሚገባ አመልክቷል፡፡

ጥናቱን ለዐዲስ አበባ የንግድ እና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት አባላት ያቀረቡት አቶ ይርጋ ተስፋዬ፣ በጥቁር ገበያው ያለው የውጭ ምንዛሪ መጠን፣ በባንኮች ካለው ከግማሽ በላይ የበለጠ ስለኾነ፣ በተጠቃሚው ተመራጭ እንደሚያደርገው አስረድተዋል፡፡ ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውሩ፣ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶችን እንደሚያስከትልም፣ ጥናት አቅራቢው አመልክተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡