የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ያጸደቀው H. Res.128 የሕግ ውሳኔ ሃሳብ እና አንድምታው

ፍጹም አቻምየለህ - የሕግ ባለሞያ

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት በአንግሊዝኛው አጠራር HRes-128 በሚል መጠሪያ የሚታወቀውንና ባለፈው ዓመት በየካቲት ወር መጀመሪያ የቀረበውን በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ረቂቅ የሕግ ውሳኔ ሃሳብ በትላንትናው ዕለት ፀድቋል።

በአገራቸው የሚታየው የሰብዓዊ መብት አያያዝ ያሳሰባቸው ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካውያን ድምጽ ሰጭዎች በተደጋጋሚ የተካሄዱትን የምስክሮች ቃል ማሰሚያ ሥነ ሥርዓቶች ጨምሮ በጉዳዩ ዙሪያ በተከናወኑ ልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ላይ ከዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ጋር በቅርበት በመስራት ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረት ሕጉ በመጨረሻው ሊጸድቅ መብቃቱ ነው የተዘገበው።

ለመሆኑ የሕግ ውሳኔ ሃሳቡ እንዲጸድቅ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ በቆዩ ወገኖች ዘንድ በተለየ ስሜት ሲጠበቅ የቆያው ይህ ውሳኔ የተወጠነለትን ዓላማ እንደምን ያሳካ ይሆን? ምን ዓይነት ጉዳዮችንስ ተፈጻሚ ያደርጋል?

በዋሽንግተን ዲሲና በአካባቢው በሕግ ሞያ የተሰማሩ እና ሂደቱንም የተከታተሉ ባለ ሞያ አወያይተናል።

የትንታኔውን ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ያጸደቀው HRes-128 የሕግ ውሳኔ ሃሳብ እና አንድምታው