ሂስፓኒክ አሜሪካውያን በምርጫው ትልቅ ድርሻ ይኖራቸዋል

Your browser doesn’t support HTML5

በ2020 ምርጫ፣ የሂስፓኒክ ማህበረሰብ አባላት፣ አብዛኛውን ቁጥር ካላቸው ነጭ አሜሪካውያን ቀጥለው ትልቁን የመራጮች ማህበረሰብ ቁጥር እንደሚይዙ ፒው የተባለው የምርምር ማዕክል አስታውቋል፡፡ የመጨረሻው ድምጽ ሊሰጥ ጥቂት ቀናት ሲቀሩት በተሰበሰበው የኤን ቢሲ እና ዎል ስትሪት ጆርናል የህዝብ አስተያየት ድምጽ፣ በሂስፓኒክ መራጮች ዘንድ፣ የቀድሞ ምክትል ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ሁለት ለ አንድ በሆነ እጅ እንደሚበልጧቸው ተመልክቷል፡፡