"አንድ እስረኛ ተመርምሮ ሲመለስ መጀመሪያ የሚቀርብለት ጥያቄ ተሰቅለህ ነበር ወይም አልተሰቀልክም?" የሚል ነው - ከእስር የተለቀቁት አቶ ሐብታሙ አያሌው።
ዋሽንግተን ዲሲ —
Your browser doesn’t support HTML5
የቃለ ምልልሱን ሁለተኛውን ክፍል ከዚህ ያድምጡ
የቀድሞው የተቃዋሚው አንድነት ፓርቲ ቃል አቀባይ በሽብር ወንጀል ተከሰው እሥር ቤት በቆዩባቸው ሁለት ዓመታት በምርመራ ሳቢያ ደረሰብኝ ያሉት ከባድ ስቃይ አሁን ለሚገኙበት የጤና ቀውስ እንደዳረጋቸው ይናገራሉ።
ወህኒ ቤቶች ውስጥ የሚፈጸሙ ጭካኔ የተሞላባቸው ልዩ ልዩ የምርመራ ዓይነቶች በአብዛኞቹ እሥረኞች ላይ ሕልፈትን ጨምሮ ለተመሳሳይ የጤና ችግሮች እንደሚዳርጉም አቶ ሃብታሙ ያስረዳሉ።
አቶ ሃብታሙ አያሌው በዚህ ፕሮግራም ላይ ስለ ምርመራ ዓይነቶች በዘረዘሩበት ወቅት የሰጡት ማብራሪያ እጅግ ዘግናኝ በመሆኑ ሕጻናት ልጆች እንዳያደምጡት የወላጆችን ትብብር እንጠይቃለን። አቶ ሃብታሙ አያሌውን ያነጋገራቸው የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ሰሎሞን ክፍሌ ነው።
Your browser doesn’t support HTML5
የቀድሞው የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው የ'ማዕከላዊ' ታሪኮች