የጉራጌ ዞን በኮማንድ ፖስት እንዲመራ ተወሰነ

Your browser doesn’t support HTML5

በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ከዛሬ ጀምሮ በክልሉ በሚመራ፣ በፌዴራል እና ደቡብ ክልል ልዩ ኃይል የተዋቀረ ኮማንድ ፖስት እንዲመራ መወሰኑን የክልሉ ሠላም እና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ።

ኮማንድ ፖስቱ የታወጀው በአካባቢው የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር በመደበኛ አሰራር ለማረጋጋት ባለመቻሉ ነው ሲሉ የቢሮው ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ለአሜሪካ ድምፅ ዛሬ ተናግረዋል።