በጎንደር የጥምቀት በዓል በተከሰተው አደጋ የሟቾች ቁጥር አሥር ደረሰ

Your browser doesn’t support HTML5

በጎንደር የጥምቀት በዓል በተከሰተው አደጋ 80 ሰዎች በጎንደር ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ህክምና እየተሠጣቸው መሆኑ ሲገለጽ የሟቾች ቁጥር 10 መድረሱን የጎንደር ከተማ ፖሊስ ማስታወቁን ጠቅሰው የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ጠቆሙ። 245 ሰዎች ውስጥ 13ቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውና አብዛኞቹ ተጎጂዎችም ላይ የእጅና እግር ስብራት እንደገጠማቸው፣ 2 ሰዎችም በፅኑ ህክምና ክትትል ላይ መሆናቸው ተገልጿል።