“ዳያስፐራ” “ዳያስፐሬይን” “መበተን/መዘራት” - ሦስተኛው የዓለም ዳያስፐራ መድረክ




የዓለም ዳያስፐራ ፎረም - 2013


Your browser doesn’t support HTML5

“ዳያስፐራ” “ዳያስፐሬይን” “መበተን/መዘራት” - ሦስተኛው የዓለም ዳያስፐራ መድረክ


የ2013 ዓ.ም የዓለም ዳያስፐራ መድረክ ዋሽንግተን ዲ.ሲ ላይ ለሁለት ቀናት ተካሂዶ ተጠናቅቋል፡፡

የዓለም ዳያስፐራ መድረክ - 2013 በዋሽንግተን ዲሲ

“አሜሪካ የፍልሰተኞች ሃገር ነች” - የዘመናዊው ሃገርና መንግሥት መሥራቾችም የዛሬ አብዛኞቹ ነዋሪዎችም ከአውሮፓ፣ ከአፍሪካ፣ ከመካከለኛውና ሩቅ ምሥራቅ እስያ፣ ከአውስትራሊያና ከላቲን አሜሪካ በየወቅቱና በየአጋጣሚው የፈለሱ ናቸው፡፡

የዓለም ዳያስፐራ መድረክ - 2013 በዋሽንግተን ዲሲ


እዚህ ውስጥ ዜግነትን ወስደው አሜሪካዊ የሆኑትም ወላጆቻቸው መሠረተ-ኢትዮጵያ የሆኑትም ወይም ኢትዮጵያዊነታቸውን እንደያዙ የአሜሪካ ነዋሪዎቹ ትውልድ ኢትዮጵያ ሁሉ ቁጥራቸው እጅግ የበዛ ነው፡፡

ዛሬ በድፍን ዩናይትድ ስቴትስ የሚኖረው ኢትዮጵያዊና ትውልድ ኢትየጵያ ቁጥር ከግማሽ ሚሊየን በላይ ይሆናል ሲባል ይሰማል፡፡

በአሜሪካ ያለው የኢትዮጵያ ዳያስፐራ ባለፉ ሰላሣ ዓመታት ውስጥ ግዙፍ ዕድገት ማሣየቱን ዋሺንግተን ዲ.ሲ የሚገኘው ነፃ ተቋም የፍልሰት ፖሊሲ ኢንስቲትዩት ያወጣው መረጃ ይናገራል፡፡

የዓለም ዳያስፐራ መድረክ - 2013 በዋሽንግተን ዲሲ

ሰኞና ማክሰኞ፣ ግንቦት 5 እና 6 / 2005 ዓ.ም በተካሄደው በዘንድሮው ሦስተኛው የዓለም ዳያስፐራ መድረክ ላይ ብዙ ስኬት ያስመዘገቡ፣ ዓለምአቀፍ ዝናን ያተረፉና ስመጥር ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ትውልድ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አሜሪካዊያን ተሣትፈዋል፡፡

የሦስተኛው የዓለም ዳያስፐራ መድረክ ስፖንሰር ከሆኑ ኩባንያዎችና የሚድያ ተቋማት መካከል የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ አንዱ ነው፡፡

ለዝርዝርና ለተጨማሪ መረጃ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡