ሊብያ ውስጥ የታሠሩ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ስደተኞች ብሦት

U.S. President Barack Obama speaks toward Myanmar opposition leader Aung San Suu Kyi, left, during a roundtable with members of parliament and civil society to discuss Myanmar's reform process in Naypyitaw, Nov. 13, 2014.

ሊብያ ውስጥ የሚገኙ ከአምስት መቶ ሃምሣ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ስደተኞች ሰሃራ በረሃ ውስጥ በሚገኝ እሥር ቤት መታጎራቸውንና እንግልት እንደሚደርስባቸው በመግለፅ አማርረዋል፡፡



የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር


Your browser doesn’t support HTML5

ሊብያ ውስጥ የታሠሩ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ስደተኞች ብሦት


ሊብያ ውስጥ የሚገኙ ከአምስት መቶ ሃምሣ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ስደተኞች ሰሃራ በረሃ ውስጥ በሚገኝ እሥር ቤት መታጎራቸውንና እንግልት እንደሚደርስባቸው በመግለፅ አማርረዋል፡፡

ስደተኞቹ በሊብያ ወታደሮች ከባድ ድብደባ ሲፈፀምባቸው መቆየቱን፣ ሴቶቹመ እንደሚደፈሩ ተናግረዋል፡፡

ስደተኞቸ በተጨማሪም በቂ ምግብ፣ ውኃ፣ የፅዳትና የንፅሕና እንዲሁም የጤና አገልግሎት እንደማያገኙ፣ የሚኖሩትም በሰሃራ በረሃ ውስጥ በተጨናነቀ ክፍል ውስጥ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር የሊብያ ተጠሪ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ስደተኞቹ በሊብያ መንግሥት ውሣኔ ወደ እሥር ቤቱ እንዲጓጓዙ መደረጉን ገልፀው እርሣቸው ግን እንደ ስደተኞች መሥሪያ ቤት ከእሥር ቤት እንዲወጡና ወደ ትሪፖሊ እንዲሄዱ ለማድረግ እየጣሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡