ዋልያዎቹ ባፋና ባፋናን መቱ

  • እስክንድር ፍሬው

“ዋልያዎች” ብራዚል ላይ እያለሙ ነው

አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ዛሬ ዕሁድ፤ ሰኔ 9/2005 ዓ.ም በተደረገው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የደቡብ አፍሪካ አቻውን ሁለት ለአንድ በሆነ ግብ አሸነፈ፡፡



ዋልያዎቹ ባፋና ባፋናን መቱ


Your browser doesn’t support HTML5

ዋልያዎቹ ባፋና ባፋናን መቱ


የኢትዮጵያ “ዋልያዎች” ብራዚል ላይ እያለሙ ነው

አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ዛሬ ዕሁድ፤ ሰኔ 9/2005 ዓ.ም በተደረገው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የደቡብ አፍሪካ አቻውን ሁለት ለአንድ በሆነ ግብ አሸነፈ፡፡

ስለ ዋልያዎቹ


በዚህ ድልም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ደቡብ አፍሪካ፣ ቦትስዋና እና መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኙበትን ምድብ በ13 ነጥብ በመምራት አንድ ግጥሚያ ቀርቶት ማጣሪያውን በመሪነት ማለፉን አረጋግጧል፡፡

የኢትዮጵያ ቡድን ደጋፊ


መጭው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግጥሚያ ከመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ቡድን ጋር አንደሚሆን ታውቋል፡፡

በመጭው የአውሮፓዊያን 2014 ብራዚል ውስጥ ለሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ግብፅና አይቮሪ ኮስትን የመሣሰሉ ጠንካራ ቡድኖች ለተከታዩ ዙር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡

የዛሬውን ድል ተከትሎ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች በፈንጠዝያና በፍንደቃ ማምሸታቸው ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ቡድን ደጋፊ


ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡