ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በአሜሪካ ፖለቲካ ይበልጥ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ

Your browser doesn’t support HTML5

“አሜሪካ ውስጥ ካሉ ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን መካከል ከስምንት አንዱ የሚኖሩት አሌክዛንድርያና አርሊንግተን ውስጥ ነው፡፡” ያሉት የቨርጂኒያው እንደራሴ ዳን ባየር፣ ትልቅ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፏቸውን እንዲያጎለብቱ መክረዋል፡፡

የህግ መወሰኛው ምክር ቤት አባል ሴናተር ማርክ ዋርነርም በመጭው ታህሳስ በሚደረገው የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያዊያንና አፍሪካዊያን ዳያስፖራ አባላት መሳተፍ ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵውያን ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ መሆኑን የገለጹት የምክር ቤት አባላቱ ይህን የተናገሩት ባላፈው እሁድ ቨርጂንያ ውስጥ በተካሄደው ሁለተኛው የኢትዮጵያዊን ዓመታዊ ፌስቲቫል ላይ ነው፡፡