የኢትዮጵያውያን ክለቦች ግጥሚያ  በዋሽንግተን ዲሲ   

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ በርካታ የኳስ ደጋፊ ያላቸው አትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግርኳስ ክለቦች በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ኦዲ ፊልድ ስታድየም የወዳጅነት ጨዋታ አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ክለቦች በአሜሪካ ለመጀመርያ ጊዜ ባደረጉት በዚህ ጨዋታም ኢትዮጵያ ቡና 2 ለ1 ማሸነፍ ችሏል፡፡ ባለፈው እሁድ የተደረገውን ይህን ጨዋታ አስመልክቶ አስማማው አየነው የሁለቱን ክለብ ተጫዋቾች ፣ አሰልጣኞችና የቀድሞ ተጨዋቾችን አነጋግሮ ተከታዩን አዘጋጅቷል፡፡