ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ሶማሌ ክልል እና ድሬዳዋ አስተዳደር ልዩ ልዩ ፕሮጄክቶችን አስመረቁ

Your browser doesn’t support HTML5

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሶማሌ ክልልና ድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ልዩ ልዩ ፕሮጄክቶችን አስመርቀዋል። የመሰረት ድንጋይም አስቀምጠዋል። ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 388 ኪሎ ሜትር የሚሸፍንንስ ጎዴን ማዕከል ያደረጉ ልዩ ልዩ የመንገድ ፕሮጄክቶችን የመሰረት ድንጋይ ሲያስቀምጡ በድሬዳዋ ደግሞ ዘመናዊ ቄራ እና የኢንዱስትሪ ፓርክ አስመርቀዋል።