“ለፈጠራችሁት መደናገጥና ለሰራችሁት ስህተት አሥር አሥር ፑሺ አፕ ስሩ” ጠ/ሚኒስትር አብይ

Your browser doesn’t support HTML5

ጠ/ሚኒስትር አብይ አሕመድና ምክትል ጠ/ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከሀገር መከላከያ የተለያየ ክፍለ ጦር ከተውጣጡ የጦር ሰራዊት አባላት ጋር ትናንት ተወያይተዋል። Ethiopian Soldiers Protesting Over Pay Meet With PM
ጠ/ሚኒስትር አብይ አሕመድና ምክትል ጠ/ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከሀገር መከላከያ የተለያየ ክፍለ ጦር ከተውጣጡ የጦር ሰራዊት አባላት ጋር ትናንት ተወያይተዋል። አባላቱ ከተጣለባቸው ሃገራዊ ሃላፊነት እና ግዳጅ ጋር ተያያዥ ጥያቄዎችን ማንሳታቸው ሲገለፅ፣ ውይይቱ ከተጠናቀቀ በኋላ “ለፈጠራችሁት መደናገጥና ለሰራችሁት ስህተት አሥር አሥር ፑሺ አፕ ስሩ” በማለት ከአዘዟዋቸው በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩም አብረዋቸው ሰርተዋል፡፡ በትናንትናው ዕለትም ኢንተርኔት ለተወሰነ ሰዓት ተቋርጦ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡