የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዕሁድ መስከረም 27 ቀን 2005 ዓ.ም የሚካሄደውን የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምርጫ በመቃወም ዓርብ መስከረም 25 ቀን 2005 ዓ.ም ከጁምዓ ሶላት ጋር ተያይዞ በዋና ከተማይቱ አዲስ አበባና ሌሎችም ከተሞች ውስጥ ተቃውሞ አሰምተዋል።
Your browser doesn’t support HTML5
Your browser doesn’t support HTML5
ብዙ ሙስሊሞች መንግሥት በምርጫዎቹ ጣልቃ እየገባ ነው ብለው እንደሚያምኑ ከአዲስ አበባ ይሰማል፡፡
የተቃውሞው ትዕይንት የተካሄደው በአዲስ አበባና በሌሎችም ከተሞች መሆኑ የተሰማ ሲሆን በአዲስ አበባው አንዋር መስጊድ የተገኙት በብዙ ሺሆች የሚቆጠሩ ሠልፈኞች ቢጫ ካርድ ይዘው “ድምፃችን ይሰማ”፤ “ዋ! ዋ!” ይሉ ነበር፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫው የሚፈፀመው በሙስሊሙ ኅብረተሰብ ዕውቅና ባልተሰጣቸው ሰዎች ነው በሚል እንዲታገድላቸው ፍርድ ቤትን ለመጠየቅ የሞከሩ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ቅሬታዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ጠበቃ አቤቱታቸውን ፍርድ ቤት እንደማይቀበል አስታውቀዋል፡፡
የኮሚቴው አባላት የሚገኙት በእሥር ላይ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
የቪኦኤ ዘጋቢዎችን ሪፖርቶች ያዳምጡ፡፡