የኢትዮጵያ ጦር ኤል-አሊ ከተማን ለቅቆ ወጣ

አሚሶም - ኢትዮጵያ/ፎቶ ፋይል

ሶማሊያ ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር ከማዕከላዊቱ ሂራን ክልል ኤል-አሊ ከተማ ለቅቆ መውጣቱ ተገለፀ፡፡

ሶማሊያ ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር ከማዕከላዊቱ ሂራን ክልል ኤል-አሊ ከተማ ለቅቆ መውጣቱ ተገለፀ፡፡

የጦሩን መውጣት ተከትሎ የአል-ሻባብ ተዋጊዎች ከተማዪቱን መቆጣጠራቸው ታውቋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ ወታደሮች ይዞታዎቻቸውን ሲለቅቁ እዚያቹ ሂራን ክልል ውስጥ በቁጥጥራቸው ሥር ከነበሩ ከተሞች መካከል ኤል-አሊ ሁለተኛ መሆኗ ነው፡፡

ሰሞኑን ኤል-አሊ አቅራቢያ በምትገኝ ሞቆኮሪን እንዲሁ ለቅቀው መውጣታቸውን የኬንያው ዴይሊ ኔሽን ጋዜጣ ዘግቧል፡፡

የኢትዮጵያ ወታደሮች ዛሬ ማለዳ ከለቀቋት ኤል-አሊ ለምን እንደወጡ ለጊዜው ዝርዝር ማግኘት ባይቻልም የእንግሊዝ የዜና ወኪል - ቢቢሲ የአል ሻባብን ራዲዮ አንዳሉስን ጠቅሶ ባሠራጨው ዜና ጦሩ ሠፍሮበት የነበረው መደብ መደብደቡን አመልክቷል፡፡

በሶማሊያ የአፍሪካ ኅብረት ጦር - የአሚሶም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ሠራዊት ኤል አሊ ከተማን ለቅቆ መውጣቱን የከተማዪቱ ከንቲባ አደን አሊ ፊዶው ለቪኦኤ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን ድምፅ ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ ጦር ኤል-አሊ ከተማን ለቅቆ ወጣ