የሃብት ምዝበራን ለመከላከል ያስችላል የተባለለትና ከከፍተኛ ባለሥልጣናት እስከ ዝቅተኛ የመንግሥት ሰራተኞች ሃብታቸውን እንዲያስመዘግቡ የሚደረግበት የኤሌክትሮኒክስ ምዝገባ ሥርዓት መጀመሩን የፌዴራሉ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ በመዲናዋ አዲስ አበባ በተደረገ የኤሌክተሮኒክስ የሃብት ምዝገባ ሥርዓት ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮችን ጨምሮ ከ50ሽህ በላይ ሰዎች ሃብታቸውን አስመዝግበዋል ተብሏል፡፡