ሦስት ኢትዮጵያዊያን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቆም እየሠሩ ነው

Your browser doesn’t support HTML5

ሦስት ኢትዮጵያዊያን ሴት ልጆች በመላ ሃገሪቱ እየተዘዋወሩ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን “በአስማት” በማስቆም ላይ ናቸው። በትምህርት ቤቶችም ሴት ልጆች ዕኩል ተሳትፎ እንዲኖራቸው ምትኀታዊ ሥራቸውን ይሠራሉ። እንዴት ከማለታችሁ በፊት ነገሩ አዲስ የአሻንጉሊት ፊልም ጭብጥ ነው - አኒሜሽን። ማርተ ፋን ደርቮልፍ ከአዲስ አበባ የዘገበችውን ሔኖክ ሰማእግዜር ያቀርበዋል።