እንዲከራከሩ ብይን የተሰጣቸው የሕግ ድንጋጌ እንዲለወጥ ታዘዘ፤ በሙስና የተከሰሱ ጉዳይም ታይቷል፡፡
አዲስ አበባ —

እንዲከራከሩ ብይን የተሰጣቸው የሕግ ድንጋጌ እንዲለወጥ ታዘዘ፤ በሙስና የተከሰሱ ጉዳይም ታይቷል፡፡

ሌሎቹን ተከሣሾች የተከሰሱባቸው የሕግ ድንጋጌዎች ተለውጠው እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል፡፡

ከነአቶ መላኩ ፈንታ ጋር የተከሰሱት የቀድሞ የሃገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ተጨማሪ ክሦች ቀርበውባቸዋል፡፡
መለስካቸው አምሃ የዛሬን የፍርድ ቤት ውሎ ዝርዝር ዘገባ ይዟል፡፡

የሽብር ፈጠራ ክሥ ተመሥርቶባቸው የታሠሩ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ጥያቄ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት
Your browser doesn’t support HTML5
የሽብር ክሥ የተመሠረተባቸው በነፃ ተለቀቁ
እንዲከራከሩ ብይን የተሰጣቸው የሕግ ድንጋጌ እንዲለወጥ ታዘዘ፤ በሙስና የተከሰሱ ጉዳይም ታይቷል፡፡

አቶ ተማም አባቡልጉ - የሕግ ባለሙያ
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ አራተኛ ወንጀል ችሎት በሽብር አድራጎት ተከስሰው ከነበሩት የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጥያቄዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትና ሌሎች ተከሣሾች መካከል አሥር ሰዎችና ሁለት ድርጅቶች መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ አሰናበተ፡፡ሌሎቹን ተከሣሾች የተከሰሱባቸው የሕግ ድንጋጌዎች ተለውጠው እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል፡፡

ፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን
15ኛ ወንጀል ችሎት ደግሞ በሙስና ወንጀል የተከሰሱትን የአቶ መላኩ ፈንታን ጉዳይ “የሚያየው ፍርድ ቤት የቱ ነው” በሚለው ጥያቄ ላይ የመጨረሻውን ውሣኔ ለማሰማት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ከነአቶ መላኩ ፈንታ ጋር የተከሰሱት የቀድሞ የሃገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ተጨማሪ ክሦች ቀርበውባቸዋል፡፡
መለስካቸው አምሃ የዛሬን የፍርድ ቤት ውሎ ዝርዝር ዘገባ ይዟል፡፡