የሳውዲ አረቢያ መንግስት ተጨማሪ የአውሮፕላን በረራዎችን ለኢትዮጵያውያን ተመላሾች መደበ

Your browser doesn’t support HTML5

በርካታ ኢትዮጵያውያን የጉዞ ሰነዳቸውን ጨርሰው የአውሮፕላን ትኬት ቢቆርጡም በአውሮፕላን በረራ እጥረት ምክንያት ሲጉላሉ ከርመዋል። ዛሬ የሳውዲ ተጨማሪ አውሮፕላኖች በሳውዲ መንግስት በመፈቀዱ ከሳውዲ ሪያድ በርካቶች ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ እንደጀመሩ በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ መሪ አቶ ሻውል ጌታሁን ለቪኦኤ ገልጸዋል። በርካታ ተመላሾች በሪያድ አውሮፕላን ጣቢያ ተራ እስኪደርሳቸው በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውንም አክለው ተናግረዋል።