ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤተመንግሥት ገቡ

  • እስክንድር ፍሬው

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሣለኝና ቤተሰባቸው ወደ አራት ኪሎው ቤተመንግሥት ገቡ

Your browser doesn’t support HTML5

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤተመንግሥት ገቡ



አቶ መለስ ዜናዊን በመተካት ከአምስት ሣምንታት በፊት ቃለ መሃላ የፈፀሙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሣለኝ ወደ አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት የታዘወሩት ከትላንትና በስቲያ ዕሁድ ነው።
አቶ ኃይለማሪያም ሥራቸውን ወዲያው የጀመሩት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በተዘጋጀላቸው ጊዜአዊ ቢሮ እንደነበር ምንጮች ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ገልፀዋል።
ከሁሉም በላይ ትኩረት ስቦ የቆየው ግን ላለፉት አምስት ሣምንታት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመኖሪያ ቤታቸው እየተመላለሱ ለመሥራት መገደዳቸው ነው።
ለዚህም ምክንያቱ የቀድሞዋ ቀዳሚት እመቤት አዜብ መስፍን ቤተመንግሥቱን ለቅቀው አለመውጣት እንደነበረ አንዳንድ መገናኛ ብዙኃን ጠቅሰዋል።
አንድ የኢትዮጵያ መሪ ከቤተመንግሥት ውጭ ሲኖር አቶ ኃይለማሪያም የመጀመሪያው እንደሆኑ በመግለፅ የተቹም ነበሩ።
ዝርዝሩን ከእስክንድር ፍሬው ዘገባ ያድምጡ።