ኦሮምያ ውስጥ እየጨመረ ባለው ሁከት ምክንያት ሺህዎች ተፈናቀሉ

Your browser doesn’t support HTML5

አማፂው የኦሮሞ ነፃነት ጦር ባለፈው ሰኔ እንደ አዲስ ጥቃት መክፈቱን ካሳወቀ ጀምሮ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኦሮምያ ክልል መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተናግሯል።

ከአማራ ክልል ይነሳሉ የተባሉ ታጣቂዎችም በሲቪሎች ላይ እንግልት በመፈጸም እንደሚወነጀሉ ተገልጿል። ባለሥልጣናቱ ሸኔ የሚሉትና በሽብርተኛነት የፈረጁት የኦሮሞ ነፃነት ጦር የቋንቋ ማንነትን የለየም ይሁን በሲቪሎች ላይ ጥቃት እንደማያደርስ ለቪኦኤ አስታውቋል።

ከአማራ ክልል ይነሳሉ የሚባሉትንና “ፋኖ” እንደሆኑ የሚነገረውን ታጣቂዎች ማግኘትም ምላሻቸውን ማካተትም አልተቻለም።

ደብረ ብርሃን ከተማ ውስጥ የሚገኝ መጠለያ ተፈናቃዮችን በየቀኑ እየተቀበለ መሆኑን አስታውቋል።

ሪፖርተራችን ሄንሪ ዊልኪንስ መጠለያው ላይ ያሉ ተፈናቃዮችን እዚያው ተገኝቶ አናግሮ ዘግቧል።