ሮቦት ፈጣሪው ወጣት

Your browser doesn’t support HTML5

ሳሙኤል መርጋ የ18 አመት ወጣት ነው። በርካታ ተንቀሳቃሽ ሞዴል ሮቦቶችን ሰርቷል። ባለፈው አመት ህንድ ከሚገኘው በሮቦት ፈጠራና በህዋ ምርምር ተሰጦ ካላቸው አለም አቀፍ ወጣቶች የስልጠና፣ ትምህርትና የሰርቶ ማሳያ ውድድር እድሎችን ከሚሰጠው ከስፔስ ዲቨሎፕመንት ኔክሰስ/Space Development Nexus/ኩባንያ ባዘጋጀው ውድድር ከ20 ወጣቶች በአንደኝነት አሸንፏል። ከሁለት ወራት በፊትም በዛው በህንድ አለም አቀፍ ውድድር በድጋሚ የአንደኝነት ደረጃ ይዞ አሸንፏል።