ለአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ውጤታማነት

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት አስርት ዓመታት ያህል ሥራ ላይ የነበረውን ሥርዓተ ትምህርት የቀየረ አዲስ ሥርዓተ ትምህርት ተቀርጿል፡፡

በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ 3.8 ሚሊዮን ህዝብ እንደተወያየበት የተነገረ ሲሆን ዘንድሮ ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ባለው የትምህርት እርከን ላይ ተተግብሯል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል፣ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ለበርካታ ዓመታት ሲነሳ የቆየውን የትምህርት ጥራት ጥያቄ ይመልሳል ብለዋል፡፡