ድምፃዊት ቤቲ ጂ በሶስት ዘርፎች ተሸለመች

Your browser doesn’t support HTML5

ከአፍሪካ ህብረት ጋር በጋራ የሚሰራው All Africa Music Awards በምህፃረ ቃል “AFRIMA” አመታዊ የሽልማት ዝግጅት ቅዳሜ ህዳር 15 2011 በጋና ኣክራ በግዙፉ ብሄራዊ አዳራሽ ለአምስተኛ ጊዜ ተካሂዷል። የአፍሪካ ህብረት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ቱሪዝም ሚኒስትር፣ ዲፕሎማቶች፣ በርካታ የጥበብ ሰዎችና አለም አቀፍ ሚዲያዎችን ጨምሮ አምስት ሺህ ተጋባዞች በምሽቱ ታድመው ነበር።