ጋዜጠኞችን አላግባብ እያሰሩ ማቆየት ፍጹም ተቀባይነት እንደሌለው የብዙኃን መገናኛ ምክር ቤቱ አሳሰበ

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት፣ ጋዜጠኞች፥ ከሕግ አግባብ ውጪ ተይዘው እየታሰሩና የሚሠሩባቸው ተቋማትም፣ ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ብርበራ እየተደረገባቸው እንደኾነ ገለጸ፡፡

ምክር ቤቱ፣ ሰሞኑን በአወጣው መግለጫ፣ “ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ በመፍቀድ ጋዜጠኞችን ማሰር፣ በምንም መለኪያ ተቀባይነት የለውም፤” ብሏል። ከሕግ አግባብ ውጪ ታስረዋል ያላቸው ጋዜጠኞች እንዲፈቱም ጠይቋል፡፡

መግለጫውን አስመልክቶ፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡት፣ የምክር ቤቱ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታምራት ኃይሉ፥ ጋዜጠኞች እየታሰሩበት ያለው መንገድ፣ ከብዙኃን መገናኛ ዐዋጁ ጋራ የሚፃረር ነው፤ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።