ኤርትራውያንና ሱዳናውያን ስደተኞች በእስራኤል

Your browser doesn’t support HTML5

ኤርትራውያንና ሱዳናውያን ስደተኞችን በሚመለከት የእስራኤል መንግስት ያወጣውን ህግ በመቃወም በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ስደተኞችና የእስራኤል ዜጎች በጋራ ተደጋጋሚ ሰላማዊ ሰልፎችን አካሂደዋል። ጩኸታችን የተወሰነ ለውጥ አስገኝቶልናል፤ መፍትሔ እስከምናገኝም እንቀጥላለን በማለት ከስደተኞቹ አንዱ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል።የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር በቅርቡ ስደተኞችን የተመለከተ የሰጡትን የተስፋ ቃል ከሰዓታት በኃላ አጥፈው አስብበታለው ማለታቸው በርካታ ስደተኞችን አሳዝኗል።