የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሴቶች መብት አያያዝ ጥያቄ

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መንግሥት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የሴቶችና ህጻናት መብት እንዲያከብሩ ጠይቋል።

ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ የሴቶችና ህጻናት የሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ያካሄደውን አጠቃላይ ግምገማ ሪፖርት አቅርቧል።

ሪፖርቱ ያተኮረው በ2014 ዓ.ም ብቻ በኢትዮጵያ በተለይ በሴቶችና ህፃናት ላይ የደረሱ ተደራራቢ ሲል የገለፀውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መሆኑን የኢሰመኮ የሴቶችና ህጻናት መብት ኮሚሽነር መስከረም ገስጥ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

ኮሚሽነሯ እንዳሉት ሪፖርቱ ቁልፍ የሆኑ አዎንታዊ እድገቶችን፣ ዋና ዋና ጉዳዮችን፣ ተግዳሮቶችን እና ምክሮችን ያካተተ ነው።